Genesis 4

1 አዳም ከሚስቱ ከሔዋን ጋር ተኛ። አረገዘችም፣ ቃየንንም ወለደች። "በያህዌ እርዳታ ወንድ አገኘሁ!" አለች።

2 በኋላም አቤልን ወለደች። አቤል እረኛ ሆነ። ቃየን ደግሞ መሬትን እያረሰ አዝዕርት ያበቅል ነበር።

3 ጊዜ አለፈ። ቃየን ካበቀለው አዝዕርት ለያህዌ ስጦታ አድርጎ አመጣ።

6 ያህዌ ቃየንን እንዲህ አለው፡ "ለምን ተናደድክ? ፊትህስ ለምን ጠቆረ?"

8 ቃየን ወንድሙን አቤልን፡ "ወደ ሜዳ እንውጣ" አለው። ብቻቸውን ሲሆኑ፣ ቃየን በአቤል ላይ ተነሳበት። ገደለውም።