Genesis 34
1 ዲና የልያ ልጅ ነበረች። አንድ ቀን በአካባቢያቸው የሚኖሩትን ወጣት ሴቶች ለማየት ወጣች።
2 ሴኬም አያት። እርሱ የኤዊያዊው የኤሞር ልጅ ነበር። ያንን አገር ይገዛ ነበር። ያዛት። በግድም ደፈራት።
3 ከዚያም ልቡ በዲና ተማረከ። ወደዳት። ለስላሳ ቃላትንም ተናገራት።
8 ኤሞርም፣ "ልጄ ልጃችሁን ወዷታል። እባካችሁ ሚስቱ ትሁን" አላቸው።
13 የያዕቆብ ልጆች ዕቅድ አወጡ። ሴኬም ዲናን ስለጎዳት፣ ለሴኬምና ለኤሞር ዋሹ።