Genesis 20

1 አብርሃም ዕቃውን ጠቅልሎ ወደ ደቡብ በረሃ ሄደ። በቃዴስና በሹር መካከል ተቀመጠ። በጌራራም እንደ መጻተኛ ኖረ።

2 እዚያ ሳለም፣ አብርሃም ሣራን እህቴ ነች ብሎ ለሰዎች ነገረ። የጌራራ ንጉሥ አቢሜሌክ ስለ እርሷ ሰማ። ወደ ቤቱም እንዲያመጧት ሰዎችን ላከ።

3 በዚያች ሌሊት አምላክ ለአቢሜሌክ በሕልም መጣ። "አንተ የሞትክ ሰው ነህ። የወሰድካት ሴት የሌላ ሰው ሚስት ነች" አለው።

14 አቢሜሌክ ለአብርሃም በጎችን፣ ከብቶችንና አገልጋዮችን ሰጠው። ለእሱ የሚሠሩ ወንዶችና ሴቶች ሰጠው። ሣራንም መለሰለት።

17 አብርሃም ስለ አቢሜሌክ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ። እግዚአብሔርም ፈወሰው። ሚስቱንም ፈወሳት። በቤቱ የሚሠሩትን ሴቶች ሁሉ ፈወሳቸው፣ እንደገናም ልጆች መውለድ ቻሉ።